Abebe Kebede

Posted on : March 29, 2020 | post in : General Knowledge |Comments Off on Abebe Kebede |

ምስጢረ ከዋክብት

Teime: TBA

ከብዙ ሽህ ዓመታት በፊት የሥነ ፈለክ ሶይንስ ሲጀመር የጨረቃን፣ የፀሐይን የፕላኔቶችንና የከዋክብትን አጓጓዝ ለመከታተል እና ለማስረዳት ነው። በአሁኑ ግዜ የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ትልቁ ሥራቸው ለምን ይህ ወይም ያ የሥነፈለክ ክስተት  ሆነ ወይም አልሆነም ? ከዋክብት እንዴት የብርሃን ምንጭ መሆን ቻሉ ? ከዋክብት ከየት መጡ ከምንስ ተስሩ ?  እያሉ መጠየቅና መልሶቻቸውን ማስላት ነው።  እንግዲህ በጥቅሉ የሥነ ፈለክ ዋናው ስራ የከክብት ሕግጋትን ማወቅና የጠፈርን ሚስጥር ፈልፍሎ ማውጣት ነው ተብሎ ቢታሰብ መልካም ነው ። በዚህ ዓይነት ሲታይ የሥነፈለክ ተመራማሪ ለመሆን ጥብቅ ተግባራዊ የሆነ የፊዚክስ የሒሳብ የኬሚስትሪና የባዮሎጂ ትምህርት አስፈላጊ ናቸው።

ይህ በዚህ እንዳለ የሰው ልጅ የሳይንስ እውቀት ኖረውም አልኖረውም ስለ ህልውናው ብዙ ጥያቄዎች ይጠይቃል  ከየት መጣሁ? ወዴት እየሄድኩ ነው?  ተፈጥሮ ምንድነው? ከየት መጣ? ማን ፈጠረው ? ለሚሉት ጥያቄዎቹ በሚገነዘበው  የተፈጥሮ ቅጥ (ፓተርን) እምነቱንና  የሚከተለውን ህብረተሰባዊ  ስርዓት ተከትሎ መልስ ይሰጣል ።ለምሳሌ የወቅቶች መቀያየር የጨረቃ መልክ መለዋወጥ የጸሃይ የጨረቃና የከዋክብት ብርሃን መለያየት የመሳሰሉት በተመልካች ላይ ከባድ የምርምር ጥያቄዎች ያስነሳሉ።  በዚህ አምድ አንድ ሰው ሊጠይቀው የሚችለውን አንድ ጥያቄ አንስተን በጥንት አባቶቻቸን የተሰጠውን መልስ እናያለን።

ጥያቄ፡ ጸሃይ ታበራለች ትሞቃለች ጨረቃና ከዋክብትም ያበራሉ ግን ብርሃናቸው ቀዝቃዛ ነው ይህ የሆነበት ምክንያቱ ምንድነው ? ይህንን ጥያቄ ለመመለስ ስማይን እንቃኝ።

 

Comments are closed.
Theme Designed Bymarksitbd